Sunday 23 November 2014

ታዋቂው አርቲስት ባልተጠና የፊልም ቀረጻ ሜካፕ በገባለት የዓይን ኮንታክት ሌንስ የተነሳ የዓይን ብርሃኑን ለአንድ ቀን አጥቶ ዋለ

ከዘላለም ገብሬ
ለፊልም ስራ ወጥቶ በለበሰው ቀረጻው የኮንታክት ሌንስ ምክንያት አይኖቹ ለአንድ ቀናት ላለማየት ችሎ ነበር ። ይህም ሊሆን የቻለው የአይን ብሌኖቹ ውስጥ ተሰክተው የነበሩት ኮንታክት ሌንስ ለፊልሙ ስራ ሲባል እንዲያጠል የታዘዘ ሲሆን የአይኖቹን ብሌኖች ላይ ጫጭረውትተንደነበርረና ለረጅም ሰአታት አይኖቹ ሲያለቅሱ እንደነበር እና ጉዳቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እየጨመረ የመጣው የአይኑ ማልቀስ ሥሜት እስከ ሆስፒታል ድረስ እንዲሄድደና በባለሙያዎች እንዲታይ ተደርጎ መድሃኒት እንዲጠቀም አዘውት ነበር “ነገ እኮ ቴአትር አለኝ” እያለ ለቲያትር ስራው የሚጨነው አበራ ጆሮ በዶክተሮቹ ጫና አንተ አይንህ እየጠፋ ስለ ነገ ቴአትር ታስባለህ ሲሉት ምላሽ ሰጥተውታል ።
shimelis abera joro
ይህ በእንደዚህ እንዳለ ችግሩ እንዲቀል በታዘዘው መዳኒት ታግዞ እስከሚቀጥለው ማለዳ እንዲቆይ ታዟል:: በዚህ የከፋ ሁኔታ የሚደርስበት ከሆነ ግን ወደ ከፍተኛ ህክምና ለኦፕራሲዮን ሊላክከንደሚችልላሳውቀውት ተለይተዋል ።ሆኖም ግን ከአንድ ቀን በሁዋላ አይኑ ዳግም ወደ እይታ ሊመለስ እንደቻለ ኢትዮጲካን ሊንክ ጠቁⶁል ። ሆኖም ግን ከጥንቃቄ ጉድለትና የባለሙያዎች ድጋፍ ባለመኖሩ ለተደረገለት የሜካፕ ስራ አርቲስት ሽመልስ አበራ የቴአትርራ አጋጆቹን ለመክሰስ አለመክሰስ የተደረገ ምን አይነት መረጃ እንዳልተገለጸ ሲሆን ፣በሃገራችን በሚደረጉት የፊልምና የቴአትር ስራዎች ላይ የሜክአፕ አርቲስት ሆነው የሚያገለግሉት በሙሉ በሙያቸው ዘርፍ ሳይሆን ያለሙያቸው በመሆኑ ለብዙ ጉዳቶች ይዳጋል ።ይህንን ደግሞ ከግንዛቤ በማድረግ ለአይንም ሆነ ለሌላ የአካል ስራ መዋል ያለበት በሙያው ላይ የተካነ መሆን ይገባዋል።
ለእያንዳንዱ የአካል ስራ እንቅስቃሴ ሙያዊ እገዛን የሚጠይቅ ሲሆን ለአንድ ፊልም ደራሲ አዘጋጅ ፣ዳይሬክተር ወይንም ሌላም ሌላም አንድን ሰው ብቻ ማእረግ በመስጠት በሚሰራበት የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ይህ ኁኔታ መቀጣጫ ሊሆናቸው የሚገባ ሲሆን ፣ሽመልስ አበራ ጉዳዩን ከምን ሊያደርሰው እንደሚችል አልታወቀም ።

No comments:

Post a Comment