Thursday 20 November 2014

ኢትዮጵያውያን ሴቶች ለምን በፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ አይሳተፉም.

Birtukan-Mideksa1                                                                          ከበደ ሀይሌ
ስለርዕስ ሙያው ባይኖረኝም በኢትዮጵያ በአጠቃላይ በአፍርካ ውስጥጉ የሴቶች ፖለቲካ ተሳትፎ እንዳነሰ ጉዳዩ በብዙ ሰዎች አዕምሮ ውስጥ ስስለሚጉላላ ካነበብኳቸው መጻህፍት ያገኘሁትንና ካለኝ የግል አመለካከት  ለአንባቢያን ለማካፈል የዚህን ርዕስ ጽንሰ ሃሳብ አሰፈርኩ፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) መሪ የነበሩት ብርቱካን ሚደቅሳ
በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሴቶች በፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ ውስን ሆኖ መታየቱ ያስደንቃል፤ ብሎም በመንግስት ስራ ላይ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ በቁጥር አናሣ ናቸው፡፡ መልሱ ግን ቀላል አይመስልም፡፡ ይህ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዲሞክራሲና የእኩልነት መብት አለ በሚባልባቸው አገሮችም ውስጥ ይህንን ያል ብዛት የላቸውም፡፡ ኢትዮጵያውያን ሴቶች እህቶቻችን እንኳን በአገር ቤት በውጭው አለም ወጥተው በሚኖሩባቸው አገሮች ባሉት የኮሚኒቲ ጽ/ቤቶች ውስጥ በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ ላይ ለመድረስ ሲጣጣሩ አይታዩም፡፡ ይህ ስርዓት መቼ ይለወጥ ይሆን?
አንዳንዶች ወንድ/ሴት ይሁን ችሎታ ካለው ሁሉም ሰው በአገሩ ጉዳይ የመሳተፍ መብት አለው ሲሉ ሌላው ወገን ደግሞ የስራ መደቡ ሳይፈጠርላቸው የመሳተፍ መብት አላቸው ማለት ብቻ በቂ አይደለም ይላሉ፡፡ምክንያቱም በመጀመሪያ ደረጃ የፖለቲካ ስርአቱ እንቅፋት ሲሆንባቸው፤ባህሉና የቤተሰብ ሐላፊነትን ስለሚያስቀድሙ ተሳትፎአቸው ውስን ይሆናል፡፡ በመሆኑም ወንዶች በሚሳተፉበት ነገር ላይ የተሳትፎቸውን ራዕይ ለማሳካት ጥረት ቢያደርጉም ውጤታማ አይሆኑም፡፡
ሴቶች ከፈለጉ በፈለጉበት ጉዳይ ውስጥ ለመሳተፍ ሙሉ ነጻነት አላቸው፡፡ነገር ግን ፍላጎት ቢኖራቸውም በጉዳዩ አይገፉበትም እየተባለ የሚነገረው ለይሰሙላ እንጂ ተግባራዊ ሲሆን አልታየም፡፡ምክንያቱም የቤተስብ ሃላፊነትና የግላቸው ችግር ስላለ ነው ይባላል፡፡ስለዚህ በመጀመሪያ የቤት ውስጥና የውጭ ችግራውን ለማቃለል ቅድመ-ፕላን ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ካለዚያ ተገለልን ወይም ዕድሉ አልተሰጠንም እያሉ ማማረራችውን ማቆም አለባቸው የሚሉም አሉ፡፡በአፍሪካ አህጉር ውስጥ የሴት መሪ ለመሆን ዕድል ያገኙ በማላዊ፤ በላቤሪያና በሌሎች አገሮች  ነው፡፡ ይሁን እንጂ በሚኒስቴርነት ደረጃ ላይ የደረሱ ብዙ አሉ፡፡በሥራቸውም አመርቂ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡
በመጀመሪያ ደረጃ በፖለቲካ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ለመድረስ ፍላጎቱ ቢኖራቸውም በትዳርና በቤተሰብ ሃላፊነት ስለሚጠመዱ ወደ ማህበራዊው ኑሮ ያደላሉ፡፡በተጨማሪም የአገራቸው የፖለቲካ ስርዓት ግፊት ያደርጋል፤የማህበራዊና የኢኮኖሚ ችግሮቻቸው ወይም ሃላፊነታቸውም ይጫናቸዋል፡፡ ለማናቸውም የእኩልነት መብት የመሰጠቱ ጉዳይ መቅደም ይኖርበታል፡፡የማህበራዊ፣የፖለቲካዊና የኢኮኖሚ ምክንያቶች ካሉበት ክልል ወጥተው በትምህርት እንዲገፉ፤ በባህል አካባቢ ያለባቸው ተጽእኖ እንዲቃለልላቸው ተደርጎ በፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ማድረግ እንዲችሉ መደረግ አለበት ብሎ አሳማኝ ማረጋገጫ የሚያቀርብ/የሚከራከር ግለሰብ ይኖራል?
ሴቶች በፖለቲካ ውስጥ እንዳይሳተፉ የሚታወቅ እንቅፋት መኖሩ ከማይካድበት ሃቅ አንዱ ጠንካራ የገንዘብ መሰረት የሌላቸው መሆኑ ነው፡፡ቢርቁት እንኳ የማይለቃቸው የቤተሰብ ሃላፊነት አለባቸው፤የባህል ተጽእኖ ሌላው የማህበራዊ ኑሮ ችግራቸው ነው፡፡ሴቶችና ወንዶች የሚሰሩአቸው የስራ አይነቶች ተለይተው በሃይማኖት ተጠቁመዋል፡፡ሴቶች በከፍተኛ ደረጃ ሊማሩ የሚገባቸው የትምህርት አይነቶች ተለይተዋል፤ስለፖለቲካ ምንነት ለማወቅ እንዲጋለጡና ሌሎችም ተዛምዶ ላላቸው ነገሮች በልጅነታቸው ግንዛቤ እንዲያገኙ አልተደረጉም፤ በሚሉትና በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ከማተኮሬ በፊት አንዳንድ ጉዳዮችን ግልጽ ማድረግ እፈልጋለሁ፡፡
በእርግጥ የተወሰኑ ሴቶች ስለአገራችን ፖለቲካ ሁኔታ እንዲያውቁ ተደርገው አስተዋጽኦ ያበረከቱ ቢኖሩም እነኝህ ሴቶች ብዙሃኑን አይወክሉም፡፡ሆኖም በአገር አቀፍ/በቀበሌ በፓርቲ ደረጃ እንዳይሳተፉ የሚያግዳቸው ነገር አለ፤ለምሳሌ በፖለቲካ ውስጥ ለመሳተፍ ጥረት ሲያደርጉ ሲታዩ፤ ንግግር ሲያደርጉ ድሮም ፖለቲካ ለሴት
117
አይሆንም፤ሴቶች ለማድቤት ስራ እንጂ ለፖለቲካ ስራ አይመጥኑም እየተባለ ሲፌዝባቸውና ድምጻቸውን በማሳማት እንዳይታወቁ ጭቆናና ተጽዕኖ ሲደረገባቸው በትምህርት አይገፉም፡፡ ወደባልትናው ስራ ላይ ትኩረት ያደርጋሉ፤ በወንዶቸ በአጭሩ ይቀጫሉ፤ ጠቃሚ ነገር ሲሰሩም ላደረጉት አስተዋጽኦ እውቅና አይሰጣቸውም/አይመሰገኑም፡፡
ለዚህ ጉዳይ አንድ በፍርድ ቤት ውስጥ የተሰማ ገጠመኜን ልጥቀስ፡፡ ባልና ሚሰት  የሆኑ ግለሰቦች  በጋራ የንግድ ድርጅት ከፍተው ሲያካሄዱ የሥራ ድርሻ ክፍፍል ያደርጋሉ፡፡ሚስት የዋጋ ተማኝ ስትሆን ባል ደግሞ እቃ አቅራቢ ሆነው ሲሰሩ ዕዳ ያለበትን አንድ ግለሰብ ከስሰው ፍርድ ቤት ቀርበው ሳለ የዕቃ ዋጋ የሚተምን ማነው? ተብለው በዳኛ ሲጠየቁ ሚስት እንደሆነች ተናገሩ፡፡ ለመሆኑ በባህል ሴት የቤት ስራ እንጂ በዋጋ ትመና ላይ ትሳተፋለች? በማለት ዳኛዋ ታዳሚውን ለፈገግታ ጋብዘዋል፡፡
በትምህርታቸው አድገው አልፎ አልፎ ከከፍተኛ የስራ ደረጃ ላይ ቢደርሱም በፖለቲካው አለም ውስጥ እጅግም ስለማይታወቁ ከፍተኛ የፖለቲካ ስልጣን ለመያዝ በተወዳዳሪነት ቀርቶ በእጩነት ደረጃ እንኳ ቀርበው አያውቁም፤መርጫ ለማሽነፍ በህዝብ ታውቀው ለመወዳደር በፓርቲ ውስጥ መታቀፍ አለባቸው፡፡ይህ በማይሆንበት ጊዜ ለወንዶች እድል ይከፍታል፤ሴቶች ከተሳተፉ ለውጥ እንደሚያመጡ ስለሚታወቅ ይህ ለወንድ ፖለቲከኞች አይዋጥላቸውም፡፡ ህዝቡም በሴቶች ላይ እምነት አይጥልም፡፡እነሱም/ሴቶችም ፍላጎት እንዳላቸው ስለማያሳውቁ በፖለቲካ አለመብሰላቸውን ያመላክታል፤ይህ የሚያሳየው የወንድ የበላይነትንና ፖለቲካና አገር ማስተዳደር ለወንዶች ብቻ ተወስኖ የተሰጠ የስራ ድርሻ አድርጎ የዓለም ህዘብ ያየዋል/ስለሚቆጥረው ይሆናል፡
የማህበራዊ ኑሮ ባህላችንና የሀይማኖት እምነታችን ሴቶችን ጨቁኖ በመያዝ ሴቶች እንደ ሁለተኛ ዜጋ ሆነው እንዲታዩ/ልጆችና ባሎቻቸውን ቀዳሚ ተንከባካቢ እንደሆኑ፤ዶልተዋል፤ የቤት እመቤት ብቻ እንዲሆኑ አስተዋጽኦ አድርገል ለማለት ያሰደፍራል፤ይህን ሁሉም ሰው ያምንበታል፤ሴቶች አስተያየታቸውና አመለካከታቸው ጠቃሚ እንዳልሆነ በባህል ስለታመነበት ድምጻቸውን እንዳያሰሙ ተደርገዋል፡፡
ይሁን እንጂ ስር ነቀል ለውጥ ማድረግ ጊዜው አሁን ነው፡፡ አገራችን ከጥንት ጊዜ አንስቶ በወንድ ተገዝታ ለህዝቡና ለአገሪቱ የጎላ ለውጥ እንዳላሳየች ታሪክ ይመሰክራል፡፡ይህ የሚያመለክተው ወንዶች ህዝብ ረግጦ ለመግዛት እንጂ አገር ለማሻሻል/ለማሳደግ ያልታደሉ መሆኑን ነው፡፡ ስለዚህ አገር የመምራቱን እድል ለሴቶች ይሰጥና ይሞከሩት፤በሌሎች አገር ከወንዶች ይልቅ ሴቶች አገራቸውን የማሻሻል አቅጣጫ ለማሳየት የበቁበቻው አሉ፤ለየት ያለ መንገድ መሞከሩ አይጎዳምና፡፡
ለምሳሌ ላቤሪያ ከብዙ አመታት ጦርነትና የምስልቅል የህዝብ ኑሮ በኋላ አገር የመምራት ፍንጭ የሌላቸውን የጦር መሬዎች አንስቶ በሴት ለመተካት በመቻሉ በብዙ የሰለጠኑ አገሮች ምስጋናን አትርፈዋል፡፡ ሳውዝ ኮሪያ፤ጀርመን ወዘተ. አፍሪካ መሪ አልተፈጠረባትም የሚለውን ለማስተባበል በአገራቸው አስችለዋል፡፡ ሰላም ለማስፈንና አንድ አድርገው ለመምራት በቅተዋል፡፡የእስያንና የአፍርካ አገሮች ለናሙና ያህል ተጠሩ እንጂ ባደጉ አገሮችም በከፍተኛ የፖለቲካ ስልጣን ላይ የወጡ አለም ያፈራቸው ከወንድ የሚበልጡ አገር የመምራት ችሎታ ያላቸው ጠንካራና ኃይለኛ ሴቶች አሉ፡፡ይህ የሚያሳየው ከወንዶች ይልቅ ሴቶች አገር የመምራት፤ የህዝብ ሰላምና መብት ጠብቀው የማስተዳደር ችሎታ እንዳላቸው ነው፡፡የስቶች ችሎታ ያልታየና ያልተነካ፤አርቆ የማየት የተፈጥሮ ሞያ ያላቸው ለመሆናቸው በባለሙያዎች ተረጋግጧል፡፡
ለሴቶች የፖለቲካና አገር የማስተዳደር ችሎታቸው በአለም ዙሪያ ታውቆላቸው ሳለ በአፍሪካ አህጉራት ግን ሴቶች ከቤት እመቤትነት ሌላ ስራ አይፈልጉም፤ ፍላጎትም የላቸውም የሚባለውን አጉል አስተሳሰብ በሰለጠነው አገር በተግባር አሰመሰክረዋል፡፡ ስለዚህ ሴቶች የወንዶችን ያህል እንደሚሰሩ ስለታወቀ ሴቶች እህቶቻችን ስለሃገራቸውና ስለፖለቲካ ተሳትፏቸው ጉዳይ ሊያሰቡበት ይገባል፡፡ አፍሪካ የወንድ የበላይነት የነገሰባት አህጉር በመሆኗ ሴቶችን በባህል ተጽእኖ መያዟ መወገድ አለበት፡፡
ሴቶች በፖለቲካ ስራ ላይ እንዲሳተፉ አገር ወዳድና አርቆ አሰተዋይ ተባባሪ የወንዶች እገዛ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ይህ ካልሆነ በቀር ሴቶች የፖለቲካ ስልጣን ላይ አይወጡም፡፡የአዋቂዎችን አባባል ስናስታውስ ”የእሳቱን ግለት ያልተቋቋመ ሰው ማእድ ቤቱን መልቀቅ አለበት” የሚባል አባባል አለ፡፡የሳትን ማቃጠል ከቻሉ ፖለቲካ መምራት ለምን ይሳናቸዋል፡፡ ከወንድ ሌላ ስለፖለቲካ ጉዳይ የሚያውቅ የለም የሚለውን የአፍሪካ ህዝብ ስለሚያምንበት በውዴታም ሆነ በግዴታ ስልጣኑን ይዞ ይቆያል እንጂ ከእሱ የተሻለ መሪ አስቀምጦ ውጤት መጠበቁ አይሆንልበትም፡፡ለምን ስልናቸውን ሌሌላ ይሰጣሉ፤ ብቅ ብቅ የሚለውንና ለአገሩ የሚያስበውን ያርቁታል፤ይህንን ለመቋቋም በተለይ ወጣቱ ትውልድ በዘመናዊ ትምህርት የመታነጽ ዕድል ስላገኘ የወንድ ፖለቲከኞችን መታገል፤የወንድ የበላይነትን ጉዳይ ማመንመን ይኖርበታል፡፡
ሴቶችም ቢሆኑ ስልጣን ይዘው ካልተሳካላቸው ሴት ስለሆኑ ብቻ እንዳልሆነ ማወቅ አለባቸው እንጂ ሴት ስለሆንኩኝ ነው የሚለውን አስተሳሰብ ከአዕምሮአቸው ውስጥ ማስወገድ አለባቸው፤ወንዶች ምን ጊዜም የበላይ ናቸው በሚለው ኋላቀር አስተሳሰብ እንዳይታለሉ፤ወንዶች የሚጫወቱትን የፖለቲካ ቁማር ለመጫወት ታጥቀው መቆም አለባቸው፡፡ ካላሸነፉ አብረው ጥሩ ስም የሚያስጠራ ስራ በመስራት ለመቆም፤ካለበለዚያ ማደግ የለምና የአስተሳሰብ ጠባብነትን ማስወገድ፤ ሴቶች ወንዶች የሚሰሩትን ማለትም ቆራጥንትን፤ብልጥነትን፤አርቆ አስተዋነት፤ ንቁነትን፤ ተባብሮ መኖርን፤ ወድቆ መነሳትን፤የወንዶች የበላይነትን አስተሳሰብን መቋቋም፤ አስተዋይነትንና አለመታለልን የአፍሪካ መሪዎች የሚጫወቱትን እሰጥ አገባ አብሮ መጨወትን፤ሆደባሻነትን፤ ሃዜኔታንና ማለቃቀስን ጠንቅቀው መረዳትና ማቆም አለባቸው፡፡
አሜሪካ ጯሂና የጾታ እኩልነት የሚያስከብር ህግ አለኝ ብትልም የአገር መሬነቱን ስልጣን ለሴቶች እስካሁን አላሰረከቡም፡፡ ወንዶችን ከመምረጥ ሴቶችን መምረጥ ያስፈልጋል የሚለው የጥንት አመለካከታቸው እሰከ 21ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ድረስ ስላልቀነሰ የመሪነቱን ወንበር ለመልቀቅ እስካሁን አልፈቀዱም፡፡ይህ በመሆኑ ኸላሪ ክሊነተን /ሳራ ፓሌን የአሜሪካ ፕሬዜዳንትነቱን ቦታ ለመያዝ እንደ አውሮፓ ቀን አቆጣጠር 2008 ዓ.ም ላይ ታግለው የውስጥ ጉዳይ በሆነ ነገር ባይመረጡም ጥሩ መሪ መሆን እንደሚችሉ የአሜሪካ ህዝብ አውቋቸዋል፡፡ ለምሳሌ ኀለሪ ክሊነትን ብንወስድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሆና ችሎታዋን በተግባር ለዓለም ህዝብ አሳይታ ተረጋግጦላታል፡፡የእሷ ምሳሌነትም በብዙ አገሮች ውስጥ ሴቶች ሥልጣን ላይ ወጥተው ችሎታቸውን እንዲያረጋገጡ አድርጓል፡፡
           
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) መሪ የነበሩት ብርቱካን ሚደቅሳ

No comments:

Post a Comment