Wednesday 26 November 2014

ጋዜጠኛውን ደብድቧል የተባለው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ በዋስ ተፈታ

(ሰንደቅ ጋዜጣ) ነሐሴ 20 ቀን 2006 ዓ.ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ገልፍ ኢዚዝ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ላይ የግል ተበዳይ በሆኑት ጋዜጠኛ ግዛቸው እሸቱ ላይ የቀላል የአካል ጉዳት አድርሰዋል ተብለው በወንጀል ተጠርጥረው ቦሌ ምድብ በመጀመሪያ ደረጃ 4 ወንጀል ችሎት ሕዳር 16 ቀን 2007 ዓ.ም ቀርበው ጉዳያቸው ተሰምቷል።
Daniel tegegne
የወንጀል ችሎቱ ግራና ቀኝ አከራክሮና የሶስት ምስክሮችን ቃል ካዳመጠ በኋላ ሕዳር 30 ቀን 2007 ዓ.ም ለብይን ቀጠሮ ሰጥቷል።
ከዚህ በፊትም በካራማራ ፖሊስ ጣቢያ ለምርመራ የተጠራው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ በቀረቡ ጊዜም በ3ሺ ብር ዋስትና መለቀቃቸው ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment