Sunday 8 March 2015

Woyanne honcho Tedros Adhanom admits that he was duped by a 14-year-old girl

March 8, 2015
schoolgirlታዳጊ በሪቱ ጃለታ አሕመድ ባገኘችው 20 ሚልዮን የአውስትሬልያ ዶላር በጋራ ሙለታ ኦሮምያ የ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት በጀመረችው ፕሮጀክት ዙሪያ ባለፈው ሳምንት ብዙ አስያየት ደርሶኛል፡፡ በወቅቱ ከግብፅና ሱዳን ጋር በአባይ ወንዝ አጠቃቀምና የህዳሴ ግንባታ ዙሪያ ድርድር ላይ ስለነበርኩና ድርድሩም የሌት ተቀን ስራ ስለነበር አስተያየታችሁን ለማየት ጊዜ አልነበረኝም፡፡ ቀደም ብየ መልስ ባለመስጠቴ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ እንደምታውቁት በሪቱ የ 14 ዓመት ታዳጊ ናት፡፡ ህፃናትና ታደጊዎች የዋሆች እንደሆኑ ክፋት እንደሌላቸው ከኔ ጋር የምትስማሙ ይመስለኛል፡፡ በዚህ ምክንያትም ህፃናትና ታዳጊዎች የሚነግሩኝን ማመን እመርጣለሁ፡፡ ስህተትም ቢኖራቸው ከየዋህነት ካልሆነ ከክፋት አይመነጭም፡፡ ህፃናትን ማመን ስህተት ከሆነ መሳሳትን እመርጣለሁ፡፡ ስለዚህ አሁንም በሪቱ ያለችውን ማመን እመርጣለሁ፡፡ ያልተገባ ነገር እየፃፍን ልጅቷን ባንጐዳ፡፡ ያሰበችው ፕሮጀክት የተቀደሰ ነው እንደሚሳካም እምነቴ የፀና ነው፡፡ አሁን ዋናው ጉዳይ በሪቱ ጃለታ አሕመድ ህልሟን እንድታሳካ የማበረታታትና የመደገፍ ነው፡፡ Galatoomaa በሪቱ፡፡ አላህ ይባርክሽ፡፡ Rabbi si haaeebbisu በርቺ፡፡ Jabaadhuu

No comments:

Post a Comment