Saturday 6 December 2014

(ሰበር ዜና) መስቀል አደባባይን በርከት ያሉ ፖሊሶችን የጫኑ የፌደራል መኪኖች አጣበዋታል; ለሰልፍ የሚወጣውን እያፈኑ ነው

ሰማያዊ ፓርቲን ጨምሮ 9ኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዛሬ በመስቀል አደባባይ የጠሩት የ24 ሰዓት የተቃውሞ ሰልፍን ለማስቆም መንግስት መስቀል አደባባይ ላይ የፌደራል ፖሊስ በጫኑ መኪናዎችን ማስፈሩን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ::
semayawi
9ኙ ፓርቲዎች መንግስት ተቃውሞውን ለማፈን ከመንገድ ላይ እያስቀረ በመሆኑ በአንድ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ከመሄድ ይልቅ በተለያያ አቅጣጫ እንዲሄድ ከደቂቃዎች በፊት ባወጡት መግለጫ ጥሪ አቅርበዋል::
በመስቀል አደባባይ የተገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እየታፈኑ ወደ ኤግዚቢሽን ማዕከል እየተወሰዱ መሆኑን የገለጹልን የአይን እማኞች ሂጃብ የለበሱ የሙስሊም ሴቶች; የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ህብረት ሊቀመንበርና የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፀሃፊ አቶ ግርማ በቀለ; አህመድ ሞሃመድ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል እና ሌሎችም ታፍነው ተወስደዋል::
በአሁኑ ወቅት መስቀል አደባባይ የሚገኘው ፌደራል ፖሊስ ለተቃውሞ የወጣውን ሕዝብ እየበተነ; እያሰረ ይገኛል::
ተጨማሪ መረጃ ይዘን እንመለሳለን::

No comments:

Post a Comment