Friday 19 September 2014

“ጋኖች አለቁና ምንቸቶች ጋን ሆኑ” – የለንደኖቹ ልማታዊ “ካኅናት” ወያኔያዊ ዘጋቢ ፊልም አቀናበሩብን!

ወንድሙ መኰንን፡ ኢንግላንድ መከረም ፯ ቀን ፪፲፻፯ ዓ.ም
መግቢያ
london Churchእንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳችሁ። መባል ስላለበት ነው። ያለፈውማ ዓመት አንደኛውን ጥቁር ዓመት ተብሏል። ሲያንሰው ነው። ወያኔ ከመቼው በበለጠ ጥቃቷን በኢትዮጵያ ልጆች ላይ በሁሉም አቅጣጫ ያጧጧፈችበት ዓመት ነበር። ነጻውን መገናኛ ብዙሀን ከጨዋታ ውጪ አድርጋለች። ብዙ ጋዜጠኞች በማሠሯ ወህኔ ቤቱ ጠቧል መሰለኝ፣ አሁን አሁን የያዘችው ዜዴ፣ በቁጥጥሯ ሥር ከሌሉ፣የፋሺን ጋዜጠኞችም ሳይቀሩ ማዘዣ ሳይደርሳቸው፣ በሬዲዮዋና በጋዜጦቿ “ከስሼአቸዋለሁ!” በማለት ፣ ነጭ ሽብር እየነዛችባቸው በርግገው ከአገር እንዲጠፉ ማሳደዷን በሰፊው ተያይዛቸዋለች። በዓመቱ መጨረሻ ወር ብቻ 21 ጋዜጠኞች ተደናብረው አገር ጥለው እግሬ አውጪኝ ብለዋል።ሲሸሹም እያየች አታስቆማቸውም። ብቻ ሲወጡላት፣ “እስየው ተሰደዱልኝ!” ብላ “ደቁሴ ንሬ፣ ተባራብሬ!”ዋን ትደልቃልች! ወንድማችን እስክንድር ነጋ፣ እህታችን ርዕዮት ዓለሙና ሌሎች ጋዜጠኞች ብዕር ስላነሱባት ተሸብራ “ሽብርተኞች” ብላ ወህኒ አጉራቸዋለች። አንዷለም አራጌ፣ በአንደበቱ፣ “ወያኔ የሰው ልጅ መብት ረጋጭ ነው” ብሎ ጮክ ብሎ በመናገሩ ተሸብራ፣ 14 ዓመት ፈርዳበት ቃሊቲ ወርዶ ፍዳውን እያየ ነው። ነፍጥ አንስቶ አንድ ሁለቱን ቢደፋማ ኑሮ፣ “እንደራደር” እያለች አፏን ታሞጠሙጥ ነበር። አሁን በቅርብ ቀን ወያኔ እያዳፋች የወሰደቻቸው እነ ኃብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳኒኤል ሺበሺ፣ አብርሀ ደስታ በቃላት ካለሆነ በጥየት የት ቦታ ነክተዋት! ዕውነትም ዓመቱ የጨለማ ዓመት ነበር። የወንጀሎች ሁሉ ወንጀል ግን፣ ወንድማችንን፣ አንዳርጋቸው ጽጌን፣ አለማቀፍ የአየር ትራንስፖርት የመንገደኞችን ደኅንነት በጣሰ ሁኔታ መጥለፏ ነው። ይኸ ወንጀል ብዙዎቻችንን ቆሽታችንን አድብኖታል። ለንደን ደብርጽዮን ቅድስት ማርያምን ከሕዝቡ ቀምተው ለወያኔ ሊያስረክቡ ለሁለት ዓመታት ጎልተው የሚሞግቱን ልማታዊ ካኅናቶቿ ግን በደስታ እያሸበሸቡ ነው። እንዲያም ዘጋቢ ፊልም ሠሩብን!
ካኅን ማነው?
ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

No comments:

Post a Comment