Sunday 31 August 2014

ካርቱም ለምትገኙ ስደተኞች በሙሉ – በሱዳን የሚገኙትን 5ቱን የወያኔ ሰላዮች/ ተላላኪዎች ይወቁ.

በሱዳን ከሚገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተላለፈ ጥሪ፦
በሱዳን ሀገር ለምትገኙ ኢትዮጽያውያን በሙሉ መብታችን ሰብአዊ ክብራችን ለዘመናት በስደት በምንኖርበት ሀገረ ሱዳን በ ዩን ኤች ሲ አር በኩል ከፍተኛ አድሎ በደል እንደሚደረግብን ለማንም ግልፅ ነው። ይሂም የኛ ዝምታና አንድነት አለመኖር እረሳችንን እንደጎዳን በማንም ይታወቃል በሕብረት በአንድነት ቆመን መብታችን ለማስከበር እንዳንታገል ያደረግን የወያኔ ረቂቅ ተንኮል መሆኑ ለማንም ግልፅ ነው። ይህንን አሳዛኝ ሕይወት ማንም በየቤቱ ይናገራወል በቅርብ በሚያውቀው ጓደኛ ጎረቤት ይወያይበታል የስደተኛ መብታችንም እንዳናስከብር እንደኛው የስደተኛ መታወቂያ የያዙ ለረዥም ዓመት በጉርብትና በመሀበር በእድር የምናውቃቸው ሁለት አይነት መታወቂያ ያላቸው እስስት ሰላዮችን ስደተኛው ማህበረሰብ በይሉኝታ እስከ ዛሬ በዝምታ ሲያልፋቸው ኖረዋል። እነሆ እሰከ ዛሬ የስደተኛ መብታችን ከመጋራት አልፎ እኛን መስለው ሲሰልሉን እያየን እየሰማን አንድ ለአምስት በሚባል በስለላ ስራ ተሰማርተው በቤተክርስትያን በእድር በጉርብትና በየፀበል ፀዲቁ በዩ ኤን ኤች ሲ አር በኮር ስደተኛው በሚገኝበት በስውር ተመድበው ሰርገው በመግባት በከፍተኛ ደረጃ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። እነዚህ ከሀዲ ባንዳዎች ሰርቶ የሚኖረውን ስደተኛ እለት በእለት እየተከታተሉ ለወያኔ ኢንባሲ ዘርፈው ለማይጠግቡ ኢትዮጽያን ሸጠው ለማይረኩ ቅጥረኞች ማንኛውንም እንቅስቃሴ ሪፖርት ያደርጋሉ። ከዚህ በኋላ ዝምታችን ሰብረን ዝምታ ለበጓም አልባጃት እንዲሉ ከዚህ በታች ስማቸው የተዘረዘሩትን ወራዳ እንደ ሚሸጥ ስጋ ምንግዜም እራሳቸውን በፍርፋሪ የሚሸጡ በፍፁም ኢትዮጽያዊ ክብር
የለላቸውን በስደተኛ ስም ስደተኛ ነን የሚሉትን ከሀዲ ባንዳዎችን ከዛሬ ጀምሮ በካርቱም በተለያዩ ቦታዎች በበሀሪ በእምድሩማን በጅሬፍ በሰሀፋ ሸሪክ በሰሀፋ ዘለጥ በጀብራ በጎዝ በዴም ውስጥ የሚገኙትን ተራ በተራ እናጋልጣለን ለግዜው።……..
የካርቱም ከተማ ከፊል ገጽታ (ፎቶ ፋይል)
የካርቱም ከተማ ከፊል ገጽታ (ፎቶ ፋይል)

1ኛ. አየልኝ ተድላ መኮነን (ኰከቤ)፡− ይህ ግለሰብ በ2005 የተቋቋመው የስደተኞች ኮሚቴ ውስጥ አባል ሆኖ እየሰራ እያለ በኮሚቴ አባላት መካከል ጠንካራ እንቅስቃሴ ያደርጉ የነበሩትን ወያኔ ሆነዋል ብሎ በማስወራትና ክፍፍል በመፍጠር ኰሚቲው እንዲፈራርስ ትልቅ ሚና ተጫውቶዋል። በዚህ ሳይቆም ከኢትዮጵያ ሸሽቶ የመጣ አንድ የግንቦት 7 ዓባል አቶ አንዱአለም የተባለ ሰውየ እዚህ ካርቱም እንዲታፈንም ከፍተኛ አስተዋጾ ካደረጉት ሰዎች አንዱ ነው። COR እና UNHCR ሲሄድ ተቃዋሚ መስሎ የሚቀርብ በተግባር ግን የወያኔ ቅጥረኛ የሆነ ግለሠብ ነው።
2ኛ. ወርቁ አለባቸው (ባሪያው) ፡− ግለሰቡ የወያኔው የማፍያ ቡድን መሪ የነበረው የመለሰ ዜናዊ የሃዘን ቀን በሚከበርበት ቀን የሟቹን ፎቶ ይዞ ምሾ ሲወርድ እና ያዙኝ ልቀቁኝ ሲል ባጋጣሚ ፎቶው ይቀደዳል ወያኔ ለመሆን ይረዳኛል ብሎ ያሰበው እለቅሶ ወያኔ በሆኑት ሆን ብለህ ነው የቀደድከው አንተ ሆዳም ዓማራ ተብሎ ተዋረደ እና ተደበደበበት። ከዛን ቀን በሆላ ጠቅልሎ እንደገባ በአደባባይ አስመሰከረ።
3ኛ. ተስፉ የሽወንድም ፡− በዘመነ ደርግ በጎንደር ውስጥ በኢሰፓ ውስጥ ሲሰራ የነበረ ሲሆን ስደት ከገባበት ጊዜ ጀምሮ በየሄደበት ወሬ በመለቃቀም ለኢንባሲው የሚያቀብል አደገኛ ወሬ አነፍናፊ የሆነ ግለሰብ ነው።
4ኛ. ሽዋየ ሲሳይ ፡− በባሏ መሞት አማራነቷን ያወቀችው ቀዳማዊ ዕመቤት እየተባለች ስትሞካሽ የነበረችው አዚብ መስፍን ሱዳን ስትመጣ በቤቷ ተቀብላ በማስተናገድ ብቻ ሳትወሰን የስለላም ስራ በመስራት ሪፖርት የምታቀርብ ናት።
5ኛ. መኪ ጉራጌው ፡− በመባል የሚታወቀ ኦምዱሩማን የሚኖር ይሂው ግለሰብ ኦምዱሩማን የሚኖሩ ስደተኞችን በማማበል ስደተኞች በኢንባሲው ውስጥ በተዋቀረው እድር እንዲሳተፉ እና የተለያየ ጥቅማጥቅም እንደሚያገኙ በማሳመን የአባላት ምልመላ ያካደርጋል። እግረመንገዱንም ለኢምባሲው በመሰለል መረጃ ያቀብላል።
ወድ ኢትዮጽያዊ እነዚህ ለሆዳቸው ያደሩ አሳልፈው እንደሰጡህ ይታወቃል ሌሎችም አንድ ለአምስት በሚል በወያኔ የስላላ መረብ የተጠረነፉ እንደተለከፈ ውሻ በየስደተኛው ቤት የሚክለፈለፉ በአማራ በትግሬ በኦሮሞ በጉራጌ በደቡብ መሀበራት ስም የተደራጁ እንዳሉ ይታወቃል እነዚህ ወገን ሀገርን የሚሸጡ ደላለዎችን በማንኛውም መልኩ ከማንኛወም ማህበራዊ ግንኙነት እንዲገለሉ ማድረግ አለብን። ከአሁን በሆላ በስደተኛው ስም መነገድ እንዲያቆሙ ልንነግራቸው ይገባል። እንደማይራሩሉልህ ይታወቃልና ስለዚህ በይሉኝታ መብታችን ና የኢትዮጽያን ክብር ከአሁን በፊት አሳልፈን የሰጠነው ይብቃል እንበላችው ! በጋራ እንዋጋቸው !!!
ይህንን በረሪ ወረቀት ኮፒ እያደረክ ያላነበበው እንዲያነበው ትብብርህን አንጠይቃለን !
ለመብትህ ለክብርህ ተነስ !!!

No comments:

Post a Comment